Invite friends and family to read the obituary and add memories.
We'll notify you when service details or new memories are added.
You're now following this obituary
We'll email you when there are updates.
Please select what you would like included for printing:
የአቶ ተካልኝ ፈለቀ በዳሶ አጭር የሕይወት ታሪክ ------/////////////////////////////////////------------- አቶ ተካልኝ ፈለቀ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም በእግዚአብሔር ፍቃድ ተጠርተው ቢሄዱም በእንግድነት በነበሩብት ዘመናቸው የሠሩትን የሕይወት ታሪካቸውን በዚህ መልክ አስፍረነዋል :- አቶ ተካልኝ ፈለቀ ከአባታቸው ከአቶ ፈለቀ በዶሶ እና ከወ/ሮ አስካላ ተሊላ በ1969 (በ1962 ዓ.ም) ተወለዱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተወህዶ ቤተ-ክርስቲያን አስተምሮት ስራዓትና ደንብ ተኮትኩቶው አደጉ እድሜያቸው ለዘመናዊ ትምህርት ሲደርስ በተወዱበት አካባቢ በሚገኝ በአሰላ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ከ1ኛ- 8ኛ ክፍል ሲከታተሉ ቆይተው በጥሩ ስነ-ምግባርና ውጤት በማስመዝገብ እና ለሌሎችም ተማሪዎች አርያ በመሆን ቀጣዩን የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን በዝዋይ አጠቃላይ ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በጥሩ ውጤት አጠናቀው ካላቸው ከፍተኛ ትምህርት ፍላጎት ቀጣይ ትምህርታቸውን ዩኒቨርሲቲ በመግባት የመጀመርያ ድግሪያቸውንና የማስተር ድግሪያቸውን በኬምስትሪ አግኝተው ከስመ ጥር ሰዎች አንዱ ሆነዋል:: ብዚህም በተማሩት ትምህርት ለ 16 ዓመታት በምንጃር ሸንኮራ ወረዳ በዓለም ጤና በደብረሲና በመምህርነት እና በርዕሰ መምህርነት በማገልገል ብዙ ተማዎችን ለሀገርና ለወገን ጠቃሚ ዜጎች እንዲሆኑ አድርገዋል :: እንዲሁም አጋንበር ህንጻታ ማርያም ቤተ-ክርስቲያን ውስጥ በአገልግሎት በገንዘብ ያዢነት ህዝብን በማስተባበር በተጨማሪም በአላቸው የስዕል ችሎታ ለቤተ-ክርስቲያን የቅዱሳትን ስዕሎችን በመሳል የበረከት ሥራ ሰርተዋል:: ከዚያም የአሜርካን የውጪ እድል አግኝተው ከባለቤ- ታቸው ከወ/ሮ ወይንሼት እና ከሁለት ወንድ ልጆቻቸውና ከአንድ ሴት ልጃቸው ጋር በመሆን ወደ አሜሪካ መተው በፍሪያስ ታክሲ ካምፖኒ እንዲሁም በተለያየ የታክሲ ካምፖኒዎች በሹፌርነት ለ 12 ዓመታት በምስጉና በተሸላሚ ሠራተኝነት አገልግለዋል:: እንዲሁም በሚኖሩበት በላስቬጋስ ከተማ በማህበራዊ ህይወት ተግባቢና ለሰዎች ለችግርም ሆነ ለደስታቸው ደራሽና ርህሩህ አዛኝ ነበሩ :: በዚህ ሁኔታ ኑሮን ሲኖሩ ሳለ ባጋጠማቸው ህመም ከ09/2020 እስከ 09/25/24 ድረስ በህክምና ሲረዱ ቆይተው መስከረም/25//24 ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም በሞት ተለይተውናል :: የወንድማችንን ነፍስ በቅዱሳን እቅፍ ያሳርፍልን ለቤተሰቡ መጽናናትን ይስጥልን !!! ከቤተሰቡ የተላለፈ መልክት -------/////////////////////////////--- አቶ ተካልኝ ባጋጠመው ህመም ወቅት በመጠየቅ አይዟችሁ ብርቱ በማለትና እስከዝችም ሰዓት አብራችሁን ላላችሁ በሐዘናችንም ለረዳችሁን ና ሀዘናችንን ለተካፈላችሁን ወገኖቻችን እግዚአብሔር ብድራችሁን ይክፈልልን ሁላችሁንም እናመሰግናለን !!! ወ/ስባት ለእግዜአብሔር !!!!
Visits: 66
This site is protected by reCAPTCHA and the
Google Privacy Policy and Terms of Service apply.
Service map data © OpenStreetMap contributors